News(ዜና የካ)

Spread the love

በ2017 በጀት ዓመት በትምህርት፣ በጤና፣ በሰላምና ፀጥታ እንዲሁም በሰው ተኮር ተግባራት የነዋሪዎቻችንን የቆዩ የአገልግሎትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት አበረታች ውጤቶችን አስመዝግበናል”!!

አቶ ብርሃኑ ረታ
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ

የካርበን ልቀትን ለመቆጣጠር “አረንጓዴ አሻራ” ወሳኝ አሰተዋጽኦ ስላለው የኢንዱስትሪ እድገትና የአረንጓዴ ልማትን በጋራ ማስቀጠል ይገባል

ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ

ሀምሌ 7/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በመካሄድ ላይ የሚገኘውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በየካ ክፈለ ከተማ ወረዳ ሁለት በሚገኘው በፈረሳይ ጉራራ መካነ-መቃብር በዛሬው ዕለት አካሂዷል።

መርሃ-ግብሩን ያስጀመሩት የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ በሀገር አቀፍ ደረጃም ሆነ እንደ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከተጀመረ ሰባተኛ ዓመት ላይ መድረሱን ገልፀው የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮም በየዓመቱ በአስቀመጠው ዕቅድ መሰረት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ እያስቀጠለ ይገኛል ብለዋል።

አቶ ጃንጥራር አባይ አክለውም እንደ ተቋም በ2017 በጀት ዓመት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ለማከናወን ባስቀመጥነው ዕቅድ መሠረት የቢሯችን አመራሮችና ሰራተኞች፣የሁሉም ክፍለ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ሰራተኞችን እንዲሁም አምራች ኢንዱስትሪዎች በጋራ በመሆን ከ 2,250 በላይ ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ አሻራችን አኑረናል ብለዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ በበኩላቸው መርሀ ግብሩ ከተጀመረ በርካታ የከተማ ተቋማት በክፍለ ከተማው የችግኝ ተከላ ሲያካሂዱ መቆየታቸውን ገልፀው ክፍለ ከተማው የጫካ ፕሮጀክት መቀመጫ እንደመሆኑ በአረንጓዴ ልማቱ ዘርፍ በስፉት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የቢሮው እና የየካ ክፍለ ከተማ አመራሮች፣ሰራተኞች፣ ከክፍለ ከተማ የዘርፉ ተቋማት አመራሮች፣አምራች ኢንዱስትሪዎች የተገኙ ሲሆን ከ490 በላይ ሰዎች ተሳትፈዋል።

በየካ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የእሁድ ገበያዎች የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረቡ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ሐምሌ 6/2017 የካ ኮሚኒኬሽን

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ 20 የሰንበት ገበያዎች የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች ለነዋሪው በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረቡ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የሰንበት ገበያው ከሳምንት ሳምንት በአቅርቦትም ሆነ በጥራት እየተሻሻለ መምጣቱን እና ለሸማቹ ማህበረሰብም የሚፈለገውን አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም በእሁድ ገበያው ሲሸምቱ ያገኘናቸው ሸማቾች ተናግረዋል።

ሸማቾቹ የሰንበት ገበያው ከዚህ በተሻለ መልኩ አገልግሎቱን አስፋፍቶ ተጠናክሮ እንድቀጥልም እያሳሰቡ እስካሁን በአገልግሎት ተጠቃሚ ያልሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አስተላልፈዋል።

በ‎ቅዳሜና እሁድ የዕረፍት ቀናት አገልግልግሎ መስጠት መጀመራችንን ያውቃሉ!!

‎የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከሰኔ 5 እስከ ጳጉሜን 5/2017 ዓ.ም ባሉት የ90 ቀናት እቅድ ውስጥ ከሚከናወኑ ተግባራት አንዱ የሆነውን ውጤታማ የአገልግሎት አሰጣጥ እውን ለማድረግ በክፍለ ከተማና በሁሉም ወረዳዎች መሬት ልማት አስተዳደር፣ ገቢዎች፣ ንግድ፣ ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ፣ ህብረት ስራ፣ ግንባታ ፍቃድና ቁጥጥር፣ በፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብትልማት ፅህፈት ቤቶች ቅዳሜ ሙሉ ቀን እና እሁድ ግማሽ ቀን አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።

‎በመሆኑም የክፍለ ከተማችን ነዋሪዎችና የአገልግሎት ተጠቃሚዎች በእነዚህ ቀናት ውስጥ አገልግሎት እንደሚሰጥ አውቃችሁ በመምጣት አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ እናሳውቃለን።

ሐምሌ 5 /2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት አመት የጥናት ሰነድ ውይይት ተካሄደ ።

ሀምሌ 05/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት አመት የጥናት ሰነድ ውይይት ተካሂዷል ።

በጥናት ሰነድ ውይይቱ ላይ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው አስራትን ጨምሮ ሌሎች የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የጥናት ሰነድ አቅራቢዎች የተገኙ ሲሆን በበጀት አመቱ የተጠኑ የጥናት ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል ።

የጥናት ሰነዶቹ በአብዛኛው ከክፍለ ከተማውም ባለፈ 12ቱንም ወረዳዎች ያቀፉ ሆነው በኪራይ ሰብሳቢነት ፣ በምቹ የስራ አካባቢ ፣ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ ፣በቅንጅታዊ አሰራርና አተገባበር ተግዳሮቶች ፣ የተገልጋዮች እርካታ ፣ የሲቪል ሰርሻንቶች እርካታ በሚሉ እና መሰል ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ላይ የጥናት ሰነዶቹ ትኩረት አድርገው ቀርበዋል ።

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ እንዳልካቸው አስራት እንደገለፁት የጥናት ሰነዶቹ ተቀባይነት ያላቸውና ብዙ የተደከመባቸው እንደመሆናቸው መጠን ተቋማዊ ለውጥ ለማስመዝገብ የሚያግዙ ናቸው ያሉ ሲሆን በተለይም ሰራተኛውና አመራሩን በአግባቡ በማሰማራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ የሚያስችል ትክክለኛና ተጨባጭ የጥናት ሰነዶች መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ እንዳልቸው በተገኘው የጥናት ግኝት መሠረትም ጥንካሬዎችን ወስዶ ክፍተቶችን ደግሞ ለመሙላት ተግባራዊ ማድረግ ይገባልም ብለዋል ።

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጫሊ ቤኛ በበኩላቸው የጥናቱ አስፈላጊነትና ዋና አላማ በበጀት አመቱ የነበሩ የስራ ላይ ተግዳሮቶችን በመለየትና በቀጣይም አሻሽሎ ለመራመድ እንዲያስችል የተደረገ ጥናት መሆኑን አስገንዝበዋል ።

ሁሉም ሲቪል ሰርቫንትም ይሁን አገልግሎት ሰጪ አካል በእውቀት ላይ ተመስርቶ ለመምራትና ለማገልገል እንዲችል ጥናቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለውና በቀጣይም የጥናት ግኝቱን ተግባራዊ በማድረግ ለምናገለግለው ማህበረሰብ ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደሚገባ አቶ ጫሊ በሰጡት ማብራሪያ ላይ አክለው የጥናቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለጥናት ውጤቱ ይበጃል ያሉትን ሀሳብ አስተያየት ጠቅሰው፤ በተቋም አቅም የተሰሩት የጥናት ውጤቶች ሊበረታቱ የሚገቡ ናቸው ያሉ ሲሆን ለጥናት ቡድኑም ምስጋናቸውን በማካፈል በቀረበው የጥናት ሰነድ ውይይት መግባባት ላይ ተደርሷል ።

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 03 በፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት አስተባባሪነት የፍሳሽ መስመሮችና የወንዝ ዳርቻ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ

ሐምሌ 05/2017 የካ ኮሙኒኬሽን

በፅዳት ዘመቻው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክ/ከተማው ፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ኋላፊ አቶ ከፍያለው ተሾመ ወረዳችንን ፅዱ እና ውብ አድርጎ ለማስቀጠል አካባቢያችንን ማፅዳት የእለት ተእለት ተግባራችን በማድረግ ፅዱ ከተማን መፍጠር ይጠበቅብናል ብለዋል።

የወረዳው ም/ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ተገኝ ፅዳት የዘመናዊነት መገለጫ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የአካባቢውን ፅዳት በመጠበቅ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የፅዳት ዘመቻው ንቅናቄው በየሳምንቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ሁሉም ሰው በፅዳት ንቅናቄ በነቂስ በመሣተፍ እንዲሁም ዘውትር አከባቢውን በማፅዳት ፅዱ፣ ውብና ማራኪ አከባቢ በመፍጠር በመጪው ክረምት ከሚከሰት የጎርፍ አደጋ መከላከል እንደሚቻል አክለው ገልፀዋል።

በፅዳት ዘመቻው የወረዳው አመራሮች ፣ የአከባቢው ነዋሪዎች፣ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች የደንብ ማስከበር አባላት እና የፅዳት ሰራተኞች ተሳትፈዋል።

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የባለጉዳይ ቀንን አስመልክቶ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጡ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ሰኔ 04/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የባለጉዳይ ቀንን አስመልክቶ እየተሰጠ ያለው የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል ።

በዛሬው ዕለት አርብ ልዩ የአገልግሎት ቀን መሆኑን በማስመልከት የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ለመመልከት እንደቻለው የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው አስራትን ጨምሮ ሌሎች የተቋማት ኃላፊዎች በጋራ ሆነው ተገቢውን የባለጉዳይ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውን አረጋግጧል ።

ከሀላፊዎች በተጨማሪም የተቋማት የቡድን አስተባባሪዎች ፣ ቡድን መሪና ባለሙያዎች ለአገልግሎት ቀኑ ከወትሮው በተለዬ መልኩ ልዩ ትኩረት ሰጥተው በማገልገል ላይ ስለመሆናቸውና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በቀላሉ የሚቀርፍ ግልጋሎት ስለመፈጠሩም በተደረገው የምልከታ ሂደት ላይ ተያይዞ ተቃኝቷል ።

ስለአገልግሎቱ ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች በበኩላቸው ለአገልግሎት ቀን ልዩ ትኩረት በመስጠት ሁሉም ተቋማት በማስተናገድ ላይ መሆናቸው አገልግሎት ፈላጊው እቅዱን ለማሳካት እንዲችል ምቹ ሁኔታን ከመፍጠሩም ባለፈ የመልካም አስተዳደር ችግርን በእጁጉ የሚቀርፍ ነው በማለት ብርቱ ሀሳብ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ቀዳማይ ልጅነትን ልማት ፕሮግራምን በተመለከተ

👉ፐሮግራሙ የከተማችንን 1.3 ሚሊዮን ህጻናትን በተለይ ደግሞ 330‚000 አነስተኛ ገቢ ካላቸው ቤተሰብ የተገኙ ህጻናት ለመድረስ ያለሙ አምስት አንኳር ኢኒሼቲቮሽን አቅደን ስንተገብር ቆይተናል።j

👉ከተቀመጡት ግቦች አንጻር የወላጆችን እና አሳዳጊዎች የምክር እና የሙያ አገልግሎት የሚሰጡ 5‚000 ሰራተኞችን በማሰማራት በ 4‚979 የመኖሪያ ብሎኮች ለሚገኙ ለ 487,544 ወላጆች/አሳዳጊዎች በየአስራ አምስት ቀኑ የቤት ለቤት የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል።

👉ለ11,900 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለድገት ውስኑነት ተጋላጭ የሆኑ ነፍሰ ጡር እና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ከ 3 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት የቀጥታ አልሚ ምግብ ድጋፍ በየወሩ ተሰጥቷል።

👉ስራውን አጠናክሮ ለመቀጠል በዚህ በጀት አመትም ከ 5ዐዐ ሚሊየን በላይ በጀት ለአልሚ ምግብ በጅተናል፡፡

👉እድሜያቸው ከ 0 እስከ 3 ዓመት የሆኑ እና በኢኮኖሚ ሁኔታቸው ለዕድገት ውሱንነት ተጋላጭ የሆኑ ህጻናት የዕድገት ሁኔታ ፕሮግራሙ በተጀመረበት ወቅት ከነበረበት 66.9% ወደ 73.1% በማደግ የ 6.2 በመቶ መሻሻል አሳይቷል።

👉በጨዋታ መልክ በማስተማር በቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ይታይ የነበረው የትምህርት ዝግጁነት ምጣኔም ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ ወደ 89.03% ከፍ በማለት የልጆች ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ ችለናል፡፡

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ማህበር የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር አንዱ የሆነውን የደም ልገሳ መርሃ ግብር አስጀመሩ

“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ”በሚል መሪ ቃል የክፍለ ከተማው ሴቶች ማህበር የደም ልገሳ መርሀ ግብር አከናውነዋል።

በመርሀ ግብሩ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የደም ልገሳ መርሀ ግብሩ ተከናውኖል።

‎Waldaan dubartoota bulchiinsa kutaa magaalaa Eekkaa sagantaa tola Ooltummaa gannaa sagantaa arjooma dhiigaa eegale.

‎Dhaadannoo “tola Ooltummaan olka’iinsa Itoophiyaaf” jedhuun waldaan dubartoota kutaa magaalaa Eekkaa sagantaa arjooma dhiigaa gaggeesse.

‎Sagantaa kana irratti hoggantoonni kutaa magaalaa Eekkaa fi aanaalee qooda fudhattoonni kan hirmaatan yoo ta’u, sagantaa arjooma dhiigaa guyyaa har’a gaggeesera.


ሀምሌ 4/2017ዓ•ም፣ የካ ኮሙኒኬሽን

በየካ ክ/ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ረታ የተመራ ቡድን በመሥሪያ ቦታዎችና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ምልከታ አደረገ

ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

በየካ ክ/ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ረታ የተመራ ቡድን በመሥሪያ ቦታዎችና በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ድንንገተኛ ምልከታ አድርጓል።

ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ረታን ጨምሮ የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው አስራትና ሌሎች የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች በምልከታው የተገኙበት ሲሆን ወጣቶችና ሴቶች በተፈጠረላቸው የሥራ መስኮች የተሰማሩበትን አግባብ በመቃኘት አበረታትተዋል።

ለወጣቶች እየተፈጠረ ያለው የሥራ ዕድል ፈጠራ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ መሆኑን በማመላከት እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በጉብኝቱ ተመላክቷል።

የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 አስተዳደር የተገልጋዮችን የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ለመጨመር ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሰራቸው ያሉ ተግባራትን በተለይ ለሰራተኞች ካፌ፣ የስፖርት ጂምናዚየም እና የተገልጋዮች ማስተናገጃ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ የአመራሮች የካቢኔ መሰብሰቢያ መለስተና አዳራሽ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

ቡድኑ በወረዳው አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በመገኘትም የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች መስተንግዶና እየተደረገ ያለን የገቢ አሰባሰብ ሂደትን ተዘዋውረው በመመልከት አበረታትተዋል። የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች ፍሬ ግብራቸውን በማሣወቅ የሚጠበቅባቸውን ዓመታዊ ግብር ክፍያቸውን በመፈጸም ላይ እንደሚገኙም አረጋግጠዋል።

መልካም ልምዶችንና ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ የጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ግባችንን ዕውን የማድረግ ትልማችንን በማሳካት የካ ክፍለ ከ11 ክፍለ ከተሞች በ2ኛ ደረጃ እንዲያጠናቅቅ ላደረጋችሁ አመራሮች በሙሉ ምስጋናዬ ከልብ ነው የረዳን ፈጣሪ ይመስገን !እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን።
አቶ ዘሪሁን ኮርሜ
የየካ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብ(online) በሚሰጥባቸው የመፈተኛ ጣቢያዎች የሙከራ ፈተና ተሰጥቷል።

የሙከራ ፈተናውን በተለያዩ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት የሚማሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የወሰዱ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል አባላትና የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮች ጋር በመሆን የሙከራ ፈተናው በተሰጠባቸው ጣቢያዎች በመገኘት ሂደቱን ተመልክተዋል።

በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ የሚሰጠው የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ስኬታማ እንዲሆን የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ የሚገኝ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን የቅርብ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

በዛሬው የሙከራ ፈተና ኮምፒውተሮች ፣ ታብሌቶች እንዲሁም ላፕቶፖች እና ሌሎች ለፈተናው የሚያስፈልጉ መሰረተ ልማቶች ዝግጁ መሆናቸውን የቢሮው ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ለነባር በጎ ፍቃደኞች በመሰረታዊ የአደጋ መከላከል ዙሪያ የማነቃቂያ ስልጠና ሰጠ

ሰኔ 6/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ ከየካ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ጋር በመተባበር ለነባር በጎ ፍቃደኞች በመሰረታዊ የአደጋ መከላከል ዙሪያ የማነቃቂያ ስልጠና ሰጥቷል።

በስልጠና መድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት ከየካ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ኢምሮ እንደገለፁት በሰዉ ልጅ ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ድንገተኛ አደጋዎች ቀድሞ መከላከል እንደሚገባ ገልፀው በክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎች የጎርፍ ሰጋት ተጋላጭነት መቀነስ ላይ በጎ ፍቃደኞችን በማሳተፍ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ገልፀው ስልጠናው ግንዛቤ ለመፍጠር ሳይሆን መጭው ክረምት በመሆኑ በጎ ፍቃደኞችን ለማነቃቃት ያለመ መሆኑን አስገንዝበዋል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ስራ አስኪያጅ አቶ ኒቆዲሞስ ቡቼ በበኩላቸው የከተማዋን የአደጋ ስጋት መቀነስ በመንግስት ብቻ የሚከናወን ሳይሆን የሁሉንም የነቃ ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው በጎ ፈቃደኞች አደጋን ቀድሞ በመከላከል የአደጋ ተጋላጭነትን በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልፀው የአደጋ ስጋት የመቀነስ ተልዕኮአቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ በመሰረታዊ የአደጋ መከላከል ዙሪያ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በስልጠናውም የአደጋ ምንነትና ዋና ዋና መንስኤዎች፣የእሳት ኬሚስትሪ፣የእሳት አጠፋፍ ዘዴዎች፣የእሳት ክፍሎች፣የእሳት ማጥፊያ መሳሪያዎች አደረጃጀት አሰራር አጠቃቀም በዝርዝር ግንዛቤ የተፈጠረ ሲሆን የተግባር ልምምድ ተደርጓል።

“ከተማችን በፍጥነት እያደገችና እየበለፀገች በመሆኑ እሱን የሚመጥን የሰላምና ደህንነት ሥራዎችን  በመሥራት ላይ እንገኛለን”!!
ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ 
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር  ቢሮ ኃላፊ

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በመንግስትና በህብረተሰቡ ትብብር ወንጀልን ለመቀነስ የመንገድ ዳር እና የውስጥ ለውስጥ መንገዶች መብራት በማስወጣት ጨለማ ቦታን ወደ ብርሀን የቀየሩ ሞዴል ብሎኮችና ቀጠናዎች የመስክ ምልከታ ተካሂዷል።

በመስክ ምልከታውም የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ፣ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ፣ የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላናን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የ10ሩም ክፍለ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት፣ ህ/ሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ፅ/ቤት፣ ስራ አስኪያጅ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የማ/ሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዲቪዥን ሀላፊዎች፣ የጸጥታ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኃላፊዎችና ኦፊሰሮች ፣ የሰላም ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንደተናገሩት ከተማችን በፍጥነት እያደገችና እየበለፀገች በመሆኑ እሱን የሚመጥን የሰላምና ደህንነት ሥራዎችን ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።

እንደ ከተማም የፀጥታ አካላት ከሰላም ሰራዊቱ ጋር እጅና ጓንት ሆኖ በመስራቱ የፅንፈኛ ሃይሉን እኩይ ሴራ በማክሸፍ ባለፉት አምስት አመታት በየ አካባቢው አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ መቻሉንም ገልፀዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ በበኩላቸው የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጨለማ በመሆናቸው ምክንያት ለተለያዩ ወንጀሎች ተጋላጭ የነበሩ አካባቢዎችን የአከባቢውን ነዋሪዎችና ባለሃብቶችን በማስተባበር መብራት ማስበራት ብቻ ሳይሆን ለነዋሪው ምቹ አካባቢ እንዲፈጠርና  በመንገዶቹ ላይ የደህንነት ካሜራዎችን በመግጠም ከአከባቢው ፖሊስ ጋር በመገናኘት ወንጀል የመከላከል ሥራውን አስተማማኝ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

ብሎክን መሰረት አድርጎ በየ አካባቢው ጨለማ ሆነው የቆዩ ዋናና የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን በቀጣይም ህብረተሰቡን በማስተባበርና በመብራት ኃይል መብራት የማስበራቱ ተግባር በሁሉም ወረዳ ተጠናክሮ
እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።

የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ደበሌ በበኩላቸው ከተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ሞዴል ብሎኮችን ለማበራከት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ጨለማ የሆኑና የፀጥታ ስጋት ሆነው የቆዩ ቦታዎች በአሁኑ ሰዓት ብርሃን ፈንጥቆባቸው ነዋሪውም በነፃነት እንዲንቀሳቀስ ማስቻሉን አብራርተዋል።

የየካን ከፍታ እናረጋግጥ አሻራችን እናኑር” በሚል መሪ ሀሳብ በህብረተሰብ ተሳትፎ እና በመንግስት ካፒታል ተሰርተው የተጠናቀቁ እና በመሰራት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ጉበኙ

ጥር 18/2017ዓ.ም

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታን ጨምሮ የክፍለ ከተማና እና የወረዳ አመራሮች በክፍለ ከተማው ስር ባሉ ወረዳዎች በህብረተሰብ ተሳትፎና በመንግስት ካፒታል የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ የትምህርት ቤት ማስፋፊያና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍል ግንባታ፣ የህፃናት መዋያ (ዴይኬር)፣ የእንጀራ ፋብሪካና የጤና ጣቢያ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን እንዲሁም የ2ኛው ዙር የኮሪደር አካል የሆነውን የየቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማትን ተዘዋውረው ጉብኝተዋል።

በጉብኝቱም የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ እንደገለፁት “የየካን ከፍታ እናረጋግጥ አሻራችን እናኑር” ብለን በጀመርነው መሰረት ቅድሚያ ለትምህርት፣ ለህፃናት እና የጤና ዘርፍን በማስቀደም ትኩረት ሰጥተን እየሰራን እንገኛለን ያሉ ሲሆን የተማሪ ጥምርታውን በማስተካከል ጥራት ያለው ትምህርት ለዜጎች ለመስጠት የሚያስችል ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል።

በህብረተሰቡ ተሳትፎና በመንግስት ካፒታል እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ 7/24 እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ ብርሃኑ ረታ አክለዋል። የትምህርት ቤት ተጨማሪ G+4 የመማሪያ ክፍል ግንባታዎቹን በ55 ቀናት አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ 7/24 እየተሰራ መሆኑን በጉብኝቱ ላይ ተገልፆል።

ፕሮጀክቶቹን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተከናወነ ያለውን ርብርብ እና የስራ ፍጥነትን ጎብኝዎቹ ያደነቁ ሲሆን ስራውን ለማጠናቀቅ 7/24 በመስራት የስራ ባህልን ከመቀየር ባለፍ የበርካታ ዜጎችን ህይዎት የቀየረ መሆኑንም አብራርተዋል። የወረዳ 01 የህፃናት ማቆያ ዴይኬር፣ የቅዱስ ማርቆስ ትምህርት ቤት፣ ህዝባዊ ሰራዊት ትምህርት ቤት፣ የወረዳ 02 ፖሊስ ጣቢያ፣ የንጋት ኮከብ ቅድመ አንደኛና መካከለኛ ትምህርት ቤት፣ አድዋ በር ቅድመ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የወረዳ 11 የህፃናት መዋያ ዴይኬር፣ የካ ወረዳ 12 ጤና ጣቢያ ማስፋፊያ ህንፃ፣ የወረዳ 12 ሸማች ህብረት ስራ ማህበር የእንጀራ ፋብሪካ፣ የካራሎ ትምህርት ቤት ተጨማሪ የመማሪያ ክፍል ግንባታ እና የወረዳ 09 የህፃናት መዋያ ዴይኬር የጉብኝቱ አካል ናቸው።

ህገ— ወጥነትን በመቆጣጠር እና አቅርቦትን በማሻሻል ገበያውን ለማረጋጋት እየተሰራ ያለው ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ

ጥር 14/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የገበያ ማረጋጋት ፣ ገቢ መሰብሰብ ፣ ህገ –ወጥ ንግድ ቁጥጥር እና የኢትዮጵያ- አዲስ አበባ ታምርት ንቅናቄ ግብረ ሀይል ያለፉት ሁለት ወር ከአስራ አምስት ቀን አፈፃፀምን በመገምገም የቀጣይ በትኩረት በሚሰሩ ተግባራት ላይ ውይይት አካሂዷል።

በውይይት መድረኩ ባለፋት ሁለት ወር ከ አስራ አምስት ቀናት ንዑስ ኮሚቴው የዋጋ ጭማሪ እንዳይከሰትና ገበያውን ለማረጋጋት በሸማች ማህበራት በኩል እየተደረገ ያለ የመሠረታዊ ሸቀጥ አቅርቦት ስራ፣ በኢትዮጵያ- አዲስ አበባ ታምርት ንቅናቄ የፍጆታ ምርቶችን አቅርቦት ፣ የገቢ ስራን ከማሳደግ እና ህገወጥ ንግድን ለመከላከል የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርት እና የቀጣይ ዕቅድ በየካ ክፍለ ከተማ ንግድ ፅህፈት ቤት ኃላፊ በአቶ አለማየሁ ማሞ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በክፍለ ከተማው በሚገኙ ወረዳዎች ዙሪያ የባዛር እና የሰንበት ገበያዎች ላይ የኢንዱስትሪ ፣የእንስሳት ተዋፅኦ እና የሰብል ምርቶች አቅርቦት ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ከእቅድ በላይ አቅርቦት ማቅረብ መቻሉ ተገልፃል፡፡

በመድረኩ የገቢ አሰባሰብ ስራዎች፣የተዘዋዋሪ ብድር አጠቃቀም እና አመላለስ በተመለከተ፣የህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ስራዎች እና የተወሰዱ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ፣በኢትዮጵያ- አዲስ አበባ ታምርት ንቅናቄ የተከናወኑ ተግባራትን ጨምሮ በግብረ ሀይሉ የተከናወኑ ተግባራት ቀርበው ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

የውይይት መድረኩን የመሩት የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሀኑ ረታ እንደገለፁት ህገ ወጥነትን በመቆጣጠር እና አቅርቦትን በማሻሻል ገበያው ለማረጋጋት እየተሰራ ያለውን ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በመግለፅ የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት የሚደረጉ ድጎማዎችን ለማሳደግ የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

አቶ ብርሀኑ ረታ አያይዘውም አያይዘውም በኢትዮጵያ- አዲስ አበባ ታምርት ንቅናቄ ላይ በልዩ ትኩረት በመስራት ነዋሪው ምርቶችን በአቅራቢያው እንዲያገኝ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልፀዋል።

ግብረ ሃይሉ በቀጣይም የምርት አቅርቦት ተደራሽነቱን አጠናክሮ የማስቀጠል ስራ እንደሚሰራ እና የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በመስጠት የክትትል እና ድጋፍ ስራዎች አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል በመድረኩ ተገልፃል፡፡

አስተዳደሩ አካል ጉዳተኞች ተደራጅተው ከሚሰሩባቸው ድርጅቶች ጋር ባጋጠሟቸው ችግሮች ዙሪያ ውይይት አደረገ፡፡

ጥር 9/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አካል ጉዳተኞች ተደራጅተው ከሚሰሩባቸው ከሀገር ጥበብ ማደራጃ እና ከአዲስ የቤትና የቢሮ እቃዎች ድርጅት ከስራ ሃላፊዎች እና ከቦርድ አባላት ጋር በስራቸው ባጋጠሟቸው የአሰራር ግድፈቶችና ችግሮች ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡

የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ እንዳልካቸው አስራት ውይይት መድረኩን የመሩ ሲሆን አካል ጉዳተኞች ተሰማርተው በሚሰሩበት ተቋማት የአሰራር ችግሮች በውይይት መፍታት እንደሚገባ በመግለፅ አስተዳደሩም እግር በእግር ተከታትሎ ችግሮችን በመፍታት የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ የድርጅቶቹ የስራ ሃላፊዎች በስራቸው እያጋጠሙ ስላሉ ጉዳዮች ለቦርድ አባላቱ በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን የቦርድ አባላቱ ውሳኔ በሚያስፈልጉ አስራሮች ላይ ሃላፊነት ወስዶ መስራት እናዳለበት አስረድተዋል፡፡

የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ማህበራዊ ጉዳይ አማካሪና የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ተወካይ ወ/ሮ መሰረት መካሻ በበኩላቸው የክፍለ ከተማው አስተዳደር እና ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ድርጅቶቹ ያሉባቸውን የአሰራር ችግሮች ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በድርጅቶቹ የስራ ሃላፊዎች የተነሱ የአሰራር ግድፈቶች እልባት በሚያገኙባቸው ጉዳዮች ላይ አቶ እንዳልካቸው አስራት የቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመስሪያ ቦታዎችና አስተዳደር ጽህፈት ቤት 368 አንቀሳቃሾችን ያቀፈ ለ112 ማህበራት የመስሪያ ቦታ ቁልፍ አስተላለፈ ጥር 9/2017ዓ.ም

የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ የመስሪያ ቦታዎችና አስተዳደር ጽህፈት ቤት 368 አንቀሳቃሾችን ያቀፈ ለ112 ማህበራት የመስሪያ ቦታ ቁልፍ አስተላልፏል። በመርሀ ግብሩ የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እንዳልካቸው አስራት እንደገለፁት ወጣቶች የተሻለ ነገን ለማየት ዛሬ ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል፣ ዛሬ የመስሪያ ቦታ የተሰጣችህ ወጣቶች በተደራጃችሁበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ ስራ በመስራት ከእራሳችህ አልፎ ለሌሎች የስራ ዕድል ለመፍጠር በትጋት መስራት ይገባችሀል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የመስሪያ ቦታዎችና አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አበባው ለሚ በበኩላቸው ማህበራቱን ውጤታማና ምርታማ እንድሆኑ ሙያዊ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር አስተዳደሩ ከጎናቸው መሆንኑ በመግለፅ ማህበራቱ በሚቀጥሉት ቀናት ውል ተዋውለው ወደ ስራ የሚገቡ መሆኑን ገልፀዋል።

በንግድ ዘርፍ 134 አባላት ያሉት ያቀፈ 69 ማህበራት፣ ማኑፋክቸሪግ ዘርፍ 46 አባላት ያሉት 9 ማህበራት እና በሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የተቀመጡ የሸገር ዳቦ ኮንቴነር 188 አባላትት ያሉት 34 ማህበር አጠቃላይ 368 አንቀሳቃሾችን ያቀፈ 112 ማህበራት የመስሪያ ቦታ ቁልፍ ተረክበዋል።

የጥምቀት በዓል ፈፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከበር የቅድመ ዝግጅት ስራውን ማጠናቀቁን የየካ ክፍለ ከተማ የፀጥታ ጥምር ግብረ—ሀይል አስታወቀ ጥር

9/2017 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ የፀጥታ ጥምር ግብረ—ሀይል የጥምቀት በዓል ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እና በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ የከተማ ደጋፊ አመራሮች በተገኙበት ተገምግሟል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን እንደገለፁት የከተራና የጥምቀት በዓል በወንድማማችነት፣ በህትም አማችነት እና በአንድነት የሚከበር በመሆኑ በዓሉ በሰላም እንዲከበር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የጥምቀት በዓል በሰላማዊ መንገድ እንዲከበር የማይፈልጉ ሀይሎችን ሴራቸውን በማክሸፍ ዘላቂ ሰላማችንን ማስቀጠል ይገባል፤ ይህ የሚሆነው ሁላችንም በቅንጅት መስራት ስንችል ነው ሲሉ አቶ በላይ ደጀን አክለዋል። የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ በበኩላቸው የከተራና የጥምቀት በዓልን ለማክበር የሚወጣው ምዕመን ምንም የፀጥታ ስጋት ሳይገባው በደስታ አክብሮ እንዲመለስ አስተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎችንና የፀጥታ አካላትን በማወያየት ቅድመ ዝግጅት ስራውን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን በመግለፅ ህብረተሰቡ ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመሆን የፀረ ሰላም ሀይሎችን ሴራ ማክሸፍ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የከተራና የጥምቀት በዓል ሀይማኖታዊ ስርዓቱን ጠብቆ እንዲከበር ከማድረግ በተጨማሪ ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት እንዲያከብር ከአጎራባች ከተሞችና ክፍለ ከተሞች ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አቶ ብርሃኑ ረታ አክለዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ሀላፊ ኮምሽነር ቴዎድሮስ ወ/ሚካኤል በበኩላቸው በዓሉ በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸውን በማንሳት በቀጣይ ቀናትም የፀጥታ ግብረ—ሀይሉ የጀመረውን ቁጥጥርና ክትትል ስራ አጠናክሮ በማስቀጠል ስምሪት የተሰጠው የፀጥታ አካል ከህብ ተሰቡ ጋር በመቀናጀት ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡም የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

ህብረተሰቡ በዓሉን ያለምንም የፀጥታ ችግር አክብሮ ወደ ቤቱ እንዲመለስ የሰላም ሰራዊቱን እና በየደረጃው ያሉን መዋቅሮችን ከፀጥታ አካላት ጋር አቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አቶ መገርሳ ገላና አፅንኦት ሰጥተውበታል። በክፍለ ከተማው 31 ደብር የሚገኝ ሲሆን 12 የታቦት ማደሪያ ቦታዎች መኖራቸውን እና በሁሉም ቦታ ዝግጅት መጠናቀቁን በውይይቱ ተገልፆል። በግምገማ መድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን፣ የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ ሀላፊ ኮምሽነር ቴዎድሮስ ወ/ሚካኤል የክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ መገርሳ ገላናን ጨምሮ የከተማ ደጋፊ አመራሮች የክፍለ ከተማና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች የፀጥታ ጥምር ግብረ ሀይል አባላት ተገኝተዋል።

የጥምቀት በዓል የህዝቦችን ትስስር በማጠናከር ፣ቱሪዝምን በማሳደግ እና ከተሞችን በማነቃቃት ረገድ ትልቅ ሚና አለው፡-አቶ ጃንጥራር አባይ

የጥምቀት በዓል የህዝቦችን ትስስር በማጠናከር ፣ቱሪዝምን በማሳደግ እና ከተሞችን በማነቃቃት ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የአዲስ አበባ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር አባይ ገለጹ፡፡

የጥምቀት በዓል በጃን ሜዳ በድምቀት ተከብሯል፡፡ በበዓሉ ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤን በመወከል መልእክት ያስተላለፉት አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጥምቀት በዓል ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በየዓመቱ በድምቀት እንዲከበር ከሀይማኖት አባቶች ጋር እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የጥምቀት በዓል በተመድ የትምህርት፣የሳይንስ እና የባህል ድርጅት ዩኔስኮ በማይዳሰሱ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታላቅ በዓል መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

በዓሉ በአዲስ አበባም ሆነ በመላው ሀገሪቱ ከዳር እስከ ዳር በታላቅ ድምቀት እየተከበረ እንዳለም አውስተዋል፡፡ አዲስ አበባ ህብረ ብሄራዊ ከተማ እንደመሆኗ የሀይማኖቶች ልዩነት እና ገደብ ሳይኖር ሁሉም በእኩል የሚስተናገዱባት ከተማ መሆኗም ገልጸዋል፡፡

በዓሉ በከተማዋ በሁሉም አድባራት ባማረ እና በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ እንደሚገኝም አውስተዋል፡፡በዓሉ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በዓለም ቅርስነት የተመዘገበ በዓል እንደመሆኑ ከተለያዩ ዓለማት የመጡ ቱሪስቶች እና ጎብኚዎች መታደማቸውንም አቶ ጃንጥራር ጠቅሰዋል፡፡

በዚህም የኢትዮጵያን እና የአዲስ አበባን ገጽታ ከፍ በማድረግ ረገድ ሁሉም ዜጋ የአምባሳደርነት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ ምክትል ከንቲባው በዓሉ በድምቀት እንዲሁም ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊቱን ጠብቆ ባማረና በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ላደረጉ የሀይማኖት አባቶች ፣ወጣቶች፣ የጸጥታ ሐይሎችና የከተማዋ ነዋሪዎች ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የከተራ እና የጥምቀት በዓል ያለምንም አደጋ ክስተት ተጠናቋል

በአዲስ አበባ በተካሄደው የከተራና የጥምቀት በዓል ምንም ዓይነት አደጋ ሳያጋጥም ተከብሮ ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

ኮሚሽን መ/ቤቱ በዓሉ ያለአደጋ ክስተት ተከብሮ እንዲያልፍ ከሀይማኖት አባቶችና ከበዓሉ አስተባባሪዎች እንዲሁም ከተለያዩ ሚዲያዎች ጋር በመሆን ህብተሰቡ ለአደጋ የሚያጋልጡ አሰራሮችን ተገንዝቦ አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክቶችን ሲያስተላልፍ ቆይቷል።

በዚህም በዓሉ ያለምንም አደጋ ክስተት ተከብሮ ማለፉን ነው ከኮሚሽን ያገኘነው መረጃ የሚያመላክተው። ከኮሚሽን መስሪያ ቤቱ የተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን ተግባራዊ በማድረግና የጥንቃቄ መልዕክቶች በማስተላለፍ ህብረተሰቡና የሚዲያ አካላት ላደረጉት አስተዋጽኦ ኮሚሽኑ ምስጋና አቅርቧል። በበዓላት ጊዜ የተደረጉ የጥንቃቄ ተግባሮች በመደበኛና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎችም ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባቸው ኮሚሽኑ አሳስቧል።

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በባለ ጉዳይ ቀን የሚሰጠው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል

ታህሳስ 23/2017ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ በተገኙበት እየተሰጠ ያለው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የነዋሪዎችን ጊዜ ጉልበትና አላስፈላጊ መጉላላት በማስቀረት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን የዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገልፀዋል፡፡ በተመሳሳይ ሌሎች የሴክተር ተቋማት አመራሮችም በቢሯቸው ተገኝተው ተገልጋዮችን በማስተናገድ ላይ መሆናቸውን ተዘዋውረን ለመመልከት ችለናል።

የባለጉዳይ ቀን የማህበረሰቡን ጥያቄ ከመመለስ አኳያ የላቀ ሚና እየተወጣ ይገኛል።

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ5ቱን የጳጉሜን ቀናት የንቅናቄ ስራ የቅድመ ዝግጅት አፈፃፀም ገመገመ

ነሀሴ 28/2016 የካ ኮሙኒኬሽንRead More

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ጃንጥራር አባይ እና የከተማ አመራሮች በዚህ ምሽት በየካ ሾላ መብራት መንገድ ዳርቻ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት ድምቀት የሚሰጡ ችግኝ በመትከል በድጋሚ አሻራቸውን አኑረዋል።Read More

“የተዘጋ በር መክፈቻ ቁልፍ እሳቤን መቀየርና ሁሌም ለለውጥ ዝግጁ መሆን ነው”!!
አቶ ብርሃኑ ረታ
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
Read More

ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ለሰጡን እውቅና እጅግ አድርገን እናመሠግናለን!!Read More

የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ከአቶ ጃንጥራር አባይ ጋር ከቤልጄም ኤምባሲ መገናኛ ያለውን የመንገድ ኮሪደር ልማትን ተዘዋውረው ጎበኙRead More

አቶ ሞገስ ባልቻ የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ በየካ ክፍለ ከተማ በ2ኛው ምዕራፍ የወንዝ ዳርቻ ልማት የሚተገበርባቸውን ቦታዎች ተዘዋውረው ጎበኙRead More

የየካ ክፍለ ከተማ ፕላን ልማት ጽ/ቤት ክፍለ ከተማውን በፕላን የሚመራ ለማድረግ እና የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በርካታ ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገለፀ

ነሀሴ 28/2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽንRead More

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት የመስመር ማዛወር ስራ ተጠናቀቀ

ግንቦት 2 /2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽንRead More

የቲቢ በሽታን ለመከላከል ለሚሰራው የቲቢ ምርመራ ዘመቻ ስራ ለዘርፉ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

መጋቢት 11/2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽንRead More

አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ማራኪ ለማድረግ በአምስት አቅጣጫ የኮሪደር ልማት ስራው እየተፋጠነ ይገኛል።

በየካ ክፍለ ከተማም የኮሪደር ልማቱ ነዋሪውን በባለቤትነት በማሳተፍ እየተከናወነ ሲሆን በዛሬው እለትም በወረዳ 07 እና 08 የመንገድ ዳር የልኬት ስራውን የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ከክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች ጋር በማጠናቀቅ ለትግበራው ዝግጁ የማድረግ ስራ ሰርቷል።

መጋቢት 11/2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮን የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ የማሳደግ ንቅናቄ መርኃ-ግብር በወረዳዎችም ተጠናክሮ ቀጥሏል

መጋቢት 11/2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽንRead More

በዶ/ር ኢርጎጌ ተስፋዬ የተመራ የፌዴራል የሱፐርቪዥን ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክ/ከተማ የመስክ ምልከታ አደረጉ ::

በሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ኢርጎጌ ተስፋዬ የተመራ በፊዴራል ደረጃ የተዋቀረው የሱፐር ቪዥን ቡድን የመስክ ምልከታ እያደረገ ይገኛል።

የሱፐርቪዥን ቡድኑ በቴክኖሎጅ እየተሰጡ ያሉ አገልግሎቶችን፣ ከተማ ግብርና ፣ ስፖርት ማዘውተሪያዎችን ፣ደይኬር እና የክ/ከተማ ተቋማት ስራዎችንም ምልከታ እያደረገ ይገኛል።

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!!!

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ጽህፈት ቤት በ6 ወር የስራ አፈፃፀም በከተማ ደረጃ ተመዝኖ ከ11ዱ ክፍለ ከተማ 2ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነRead More

ባለጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ እየተሰጠ ያለው አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጥር 15 /2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽንRead More

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ፅህፈት ቤት ለወጣቶች ሲሰጥ የቆየውን የህይወት ክህሎት ስልጠና ተጠናቀቀRead More

አስተዳደሩ በከተራ፣ ጥምቀት እና ቃና ዘገሊላ በዓላት አከባበር ወቅት የተሰሩ የጸጥታ ሥራዎችን ገመገመ

ጥር 13/2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በክፍለ ከተማው የከተራ፣ ጥምቀት እና ቃና ዘገሊላ በዓላት አከባበር ወቅት የተሰሩ የጸጥታ ሥራዎችን ከከተማ ደጋፊዎች፣ከክፍለ ከተማ እና ከወረዳ የስራ አመራሮች ፣ከፀጥታ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር በጋራ ገምግሟል።Read More

የምስጋና መልዕክት!

የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ ክብረ በዓል በክፍለ ከተማችን በሁሉም የታቦታት ማደሪያዎች በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ታቦታቱም በሰላም ወደ መንበረ ክብራቸው ተመልሰዋል።Read More

ለወረዳና ለክ/ከተማ ባለሞያዎች ስልጠና ተሰጠ

የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ጽ/ቤት በ3 የስልጠና አርስት ላይ ማለትም 1.webmail 2. acronis True lmage 3. A.A complaint management portal / የካ ክፍለ ከተማ የአይሲቲ ባለሙያዎች እና ለወረዳ የአይሲቲ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰቷል፡፡
ሕዳር 27/2016 ዓ.ም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ጽ/ቤት

ዜና ሹመት

አቶ ብርሃኑ ረታ አበጋዝ የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም የካ ኮሙኒኬሽን

የአቶ ብርሃኑ ረታ አጠቃላይ የስራ ልምድ፣ የትምህርት ዝግጅት እና ለሃገራቸው ያበረከቷቸውና እያበረከቱት ያለውን እንቅስቃሴ ለምክር ቤቱ አባላት በክፍለ ከተማው የመንግስት ተጠሪ ሃላፊ በአቶ መገርሳ ገላና ቀርቦ ሃሳብ ከተሰጠበት በኃላ በሙሉ ድምጽ ሹመቱ ፀድቋል።

አቶ ብርሃኑ ረታ የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው ተሾሙRead More

ዜና ጉብኝት

የየካ ክ/ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በመንግስት ካፒታል እየተገነቡ ያሉ የመንግስት ፕሮጀክቶችን ያሉበትን ደረጃ ተዘዋውረው ጉኝተዋል።Read More

የክፍለ ከተማው ተቋማት በቅንጅታዊ ትብብር አሰራር ላይ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ

በየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅህፈት ቤት በተመራው የፊርማ ስነ ስርአት ተቋማት በቅንጅት እና በትብብር በጋራ በሚያሰራቸው ጉዳይ ላይ የትስስር ሪፖርት አቅርበው የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።Read More